Agrégateur de contenus

null “የሰላም ብሔራዊ በጎ ፈቃድ የማኅበረሰብ አገልግሎት በማንነቶች ላይ መሠረት አድርጎ ያለውን መከፋፈልና ጥርጣሬ በማስወገድ የወጣቶችን የሀገርና የሕዝብ ፍቅር ለማሳደግ ከፍተኛ ሚና እያበረከተ ነው፡፡” ክቡር አቶ ቸሩጌታ ገነነ

ግንቦት 3 ቀን 2016 ዓ.ም የወጣቶች በጎ ፈቃድ ማኅበረሰብ አገልግሎት ለ9ኛ ዙር በጅማ ዩኒቨርሲቲ ስልጠና የወሰዱ ሰልጣኞች ስልጠናውን በስኬት አጠናቀው ተመርቀዋል፡፡

በስልጠናው የተሳተፉት ከሁሉም የሀገራችን ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የተወጣጡ፤ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ወጣቶች ናቸው፡፡ ወጣቶቹ ሀገራችን ሲያጋጥሟት የነበሩትን አፍራሽ አስተሳሰቦች ሰብረው ኢትዮጵያዊ ፍቅርን ተላብሰው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በመስጠት ለሀገራዊ የሰላም ግንባታ እና ብሔራዊ መግባባትን የሰላም አምባሳደርነት ሚና የመወጣት ዓላማ ያነገቡ በጎ ፈቃደኞች ናቸው፡፡

 

በምረቃው መርሐ ግብር ክቡር አቶ ቸሩጌታ ገነነ በሰላም ሚኒስቴር የፌደራሊዝምና ግጭት አስተዳደር ዘርፍ ሚኒስትር ዴዔታ ተገኝተው ባስተላለፉት መልእክት ዘላቂ ሰላም፤ የዜግነት ክብር እና ኅብረ-ብሔራዊ አንድነት ዐድጎ የማየት ርዕይን ቀርጾ የዜጋውን፣ የማኅበረሰቡን እና የቤተሰቡን ሰላም በማስጠበቅና በማስከበር፤ ብሔራዊ መግባባትን፣ ሀገራዊ አንድነትን በማሳደግ የፌደራል ሥርዓቱን በማጠናከር፣ ቀጠናዊና አህጉራዊ ትብብርን በማጎልበት አዎንታዊ ሰላምን ለማሰፈን ከሚደረግ ጥረት ቁልፍ ጉዳዮች መካከል የሰላም ብሔራዊ የበጎ ፈቃድ የማኅበረሰብ ልማት አገልግሎት በዋናነት የሚጠቀስ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጀማል አባፊጣ (ዶ/ር) “የሰላም ብሔራዊ የበጎ ፈቃድ የማኅበረሰብ ልማት አገልግሎት ፕሮግራም ወጣቱን በአመለካከትና በሥነ-ምግባር እንዲታነጽ ከማድረግ ባሻገር ብቁ ዜጋን ማፍራት የሚያስችል ብሎም በሰላም ግንባታ ሂደት ውስጥ ወጣቶች ሀገራችንን እና ማኅበረሰባችንን እንዲያውቁ፣ እንረዱና የሀገር ፍቅር ስሜት በውስጣቸው እንዲሰርጽ የሚያደርግ ስለሆነ በተሰማሩት መስክ ሁሉ ማኅበረሰብን በእውነትና በዕውቀት በማገልገል ለታዳጊዎችና ለሌሎች ወጣቶች መልካም አርአያ የሚሆኑበት ነው” ብለዋል፡፡

ተመራቂዎቹ የሰላም ብሔራዊ የበጎ ፈቃድ የማኅበረሰብ ልማት አገልግሎት ተሳታፊዎችም በሚሰማሩባቸው የሀገሪቱ አካባቢዎች ሁሉ የማህበረሰብ ልማት አገልግሎት በመስጠት በሀገር ግንባታው የራሳቸውን አሻራ ለማሳረፍ መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል፡፡

Les assets les plus vus

null ሀገራዊ የግጭት ክስተቶች ፣መንስኤዎችና የመፍትሄ አቅጣጫዎች "ላይ የተካሄደ ጥናት ውጤት ይፋ ተደረገ

ኅዳር 23/2016 . (የሰላም ሚኒስቴር)፣ "ሀገራዊ የግጭት ክስተቶች ፣መንስኤዎችና የመፍትሄ አቅጣጫዎች "ላይ የተካሄደ ጥናት ውጤት ይፋ የማድረግ መርሃ -ግብር ተካሄዷል።

በመርሃ-ግብሩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሰላም ሚኒስቴር የሰላም ግንባታ እና ብሔራዊ መግባባት ዘርፍ ሚኒስትር ዴዔታ ክቡር አቶ ታዬ ደንደአ በሀገራችን 2010 . እስከ 2015 . ድረስ በተለያዩ ክልሎች በተለያዩ ምክንያቶችና የግጭት መንስኤዎች የሚከሰቱ ግጭቶች ወደ ሁከትን እና ብጥብጥ አድገው ከፍተኛ ጉዳት በሰውና በንብረት ሲያደርሱ ቆይተዋል፤ እያደረሱም ነው ብለዋል፡፡

የሰላም ሚኒስቴር እነዚህ የሚስተዋሉ ግጭቶችንና አለመግባባቶችን ለመፍታት በተናጠል ከመስራት ማህበረሰባዊ ለውጥ ሊያመጣ በሚያስችል መንገድ ሁሉንም ዜጎችና ባለድርሻ አካላትን በማስተባበር ጥናቶችን ሲያካሂድ ቆይቷል በማለት ክቡር ሚኒስትር ደኤታው ገልፀዋል  ፡፡

አክለውም በዛሬው ዕለት ይፋ የሚደረገው ጥናት ዋና ዓላማ እና አስፈላጊነት በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚከሰቱ ግጭቶች መንስዔዎቻቸውን በመለየት፤ በቴክኖሎጂ የታገዘ የግጭት ቅድመ ማስጠንቀቂያና ምላሽ ስርዓትን በመዘርጋት ግጭቶችን ከመከሰታቸው በፊት መከላከል፣የህብረተሰቡን በሰላም የመኖር ልምድ በመጠቀም እና የሚከሰቱ ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ በመፍታት የዘላቂ መፍትሄ አማራጮችን መጠቆም ነው ብለዋል ፡፡

''ሀገራዊ የግጭት ክስተቶች ፣መንስኤዎችና የመፍትሔ አቅጣጫዎች'' በሚል ርዕስ ጥናት ያቀረቡት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የኢትዮጰያ ጥናትና ምርምር ተቋም ተባባሪ ፕሮፌሰር እና የምርምር  ክፍል ኃላፊ የሆኑት / ደሳለኝ አምሳሉ  ናቸው።

/ ደሳለኝ በጥናታቸው በኢትዮጵያ (2018-2022 ..) የተከሰቱ ግጭቶች መንስኤዎችና የመፍትሄ ሃሳቦችን በዝርዝር  አስቀምጠዋል።

ጥናቱ በኢትዮጵያ የተነሱ ግጭቶች በየትኞቹ የሀገራችን ክፍሎች በብዛት ተስተዋል የሚለውን የሚያሳይ የግጭት ፍኖተ ካርታ/conflict mapping/ የያዘ ሲሆን የተከሰቱ ግጭቶች መሰረታዊ እና አባባሽ ምክንያቶችን እና ምን ቢደረግ ግጭቶች ሊቀንሱ ይችላሉ ሚለውን ሃሳብ አስቀምጧል።

በሰላም ሚኒስቴር የፌዴራሊዝምና ግጭት አስተዳደር ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር / ስዩም መስፍን የሰላም ሚኒስቴር በተሰጠው ስልጣን መሰረት ግጭቶች መንስኤዎችን አጥንቶ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን በጥናት ለይቶ የማቅረብ ስራ እንደሚሰራ ገልፀው ዛሬ ይፋ የተደረገው ጥናት ከተለያዩ ባለ ድርሻ አካላት በጋር በመሆን የተካሄደ እንደሆነ እና ከትግራይ ክልል በስተቀር ጥናቱ ሁሉንም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ያካተተ መሆንንአስገንዝበዋል፡፡

በህዝብ ተወካዮች ምክርቤት የሰላምና የውጭ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ አመራሮችና የኮሚቴ አባላት ፣የሰላም ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮችና ባለሙያዎች ፣የፌዴራልና የክልል የመንግስት ተቋማት ኃላፊዎች እና የባለድርሻ አካላት አመራሮች በፕሮግራሙ ተሳታፊ ሆነዋል፡፡