" ወጣቶችን ያማከለ የፀረ- ሙስና ትግል የነገን ስብዕና ይገነባል " በሚል መሪ ሃሳብ ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን ተከበረ

[#if smallImage??]
    [#if smallImage?is_hash]
        [#if smallImage.alt??]
            ${smallImage.alt}
        [/#if]
    [/#if]
[/#if]

ኅዳር 26 ቀን 017 ዓ.ም የሰላም ሚኒስቴር አመራሮችና ሰራተኞች "ወጣቶችን የማከለ የፀ-ረሙስና ትግል የነገን ስብዕና ይገነባል" በሚል መሪ ሃሳብ ለ21 ኛ ጊዜ የሚከበረውን ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን በደማቅ ዝግጅት አክብረዋል።

በፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የሰላም ሚኒስቴር የሰላም ግንባታ እና ብሔራዊ መግባባት ዘርፍ ሚኒስትር ዴዔታ ክቡር ከይረዲን ተዘራ (ዶ/ር ) ሙስና ለሀገራችን ሰላም እና ልማት ትልቅ ተግዳሮት ነው ያሉ ሲሆን የፀረ ሙስና ትግል የሁሉንም ተሳትፎ እና እርብርብ ይጠይቃል ብለዋል።

የዘንድሮ የፀረ ሙስና ቀን ወጣቶችን ያማከለ አድርጎ መከበሩ ትልቅ ትርጉም አለው ያሉት ክቡር ከይረዲን ተዘራ ወጣቶችን ለፀረ ሙስና ትግል እና ለሀገር ግንባታ ስራችን ማዋል ያስፈልጋል ብለዋል።

'' ከሙስና የፀዳች ኢትዮጵያ'' የሚል ሰነድ የሰላም ሚኒስቴር የስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መንግስቱ አበራ በኩል ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

May be an image of 1 person and eyeglassesለተነሱ ሃሳቦች ማጠቃለያ የሰጡት የሰላም ሚኒስቴር የፌዴራሊዝም እና ግጭት አስተዳደር ዘርፍ ሚኒስትር ዴዔታ ክቡር አቶ ቸሩጌታ ገነነ የአንድ ሀገር ቀጣይነት የሚረጋገጠው ነፃ እና ገለልተኛ ተቋማት ሲኖሩ መሆኑን ገልፀው የአገረ መንግስቱ አንዱ ቁልፍ ችግር ነፃ፣ ገለልተኛና ማህበረሰቡን የሚጠብቁ ተቋማት ሳይገነቡ መቆየታቸውን ገልፀው በዚህ በኩል መንግስት ትልልቅ ሪፎርሞችን እያደረገ ይገኛል ብለዋል።May be an image of 7 people, dais and text

ሙስናን ለመታገል ጠንካራ ተቋማት እና የአስተሳሰብ ለውጥ ያስፈልጋል ያሉት ክቡር አቶ ቸሩጌታ ሙስናን መታገል ንብረትን ከዘረፋ እና ብክነት መጠበቅ ብቻ ሳይሆን ሀገር የመገንባት ስራ ነው ብለዋል።