በሀገሪቱ ዘላቂ ሰላምና ብሔራዊ መግባባት ይረጋገጥ ዘንድ በትኩረት እንደሚሠራ የሰላም ሚኒስቴር አስታወቀ።
Beágyazott alkalmazások
Tartalom megjelenítő
ጥር 2 /2016 ዓ.ም በ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን 11ኛ መደበኛ ጉባዔ የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር አቶ ብናልፍ አንዱዓለም ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።

የምክር ቤቱ አባላት በኢትዮጵያ ያለውን የፀጥታ ችግር በሚመለከት የተለያዩ ጥያቄዎችን ያቀረቡ ሲሆን፤ በአማራ እና ኦሮሚያ ክልል ያለውን ግጭት በሚመለከት በትኩረት የተነሱ ጥያቄዎች ናቸው::

ክቡር ሚኒስትሩ ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ሰፊ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን፤ በሀገራችን ዘላቂ ሰላም ይመጣ ዘንድ እያንዳንዱ ዜጋ የድርሻውን መወጣት እንዲሚገባው አሳስበው፤ ነገር ግን የጦርነት ነጋሪት እየጎሰሙ ሰላምን ማምጣት እንደማይቻል አስረድተዋል።

ጦርነት የትኛውንም ችግር እንደማይፈታና ቀደም ሲል በስሜኑ የሀገራችን ክፍል የተከሰተውም ሆነ አሁን በአማራ እና ኦሮሚያ ክልል ያለው ግጭት ጦር የሚያማዝዙ ሳይሆን በውይይትና በድርድር ሊፈቱ እንደሚችሉም አብራርተዋል።

ኦሮሚያ ክልል ከሚንቀሳቀሰው የሸኔ ታጣቂ ቡድን ጋር ለመደራደር መንግስት ተደጋጋሚ ሙከራዎችን አድርጎ ያልተሰካ ቢሆንም፤ የተፈለገው ሰላም እስኪሰፍን መንግስት ለውይይት ዝግጁ እንደሆነ ነው አቶ ብናልፍ የተናገሩት።
የጦርነት መቋጫው ድርድር በመሆኑ በኦሮሚያም ሆነ በአማራ ክልል ያሉ ታጣቂዎች ተጨማሪ ዋጋ ሳይከፈል ወደ ሰላማዊ መንገድ እንዲመጡ የሰላም ሚኒስትሩ ጥሪ አቅርበዋል።
በጋምቤላ እና ቤኒሻንጉል ክልል በተሰራው ስራ በክልሎቹ የሚንቀሳቀሱትን ታጣቂዎች ወደ ሰላማዊ መንገድ በማምጣት ተስፋ ሰጪ ስራዎች መሰራታቸውን አቶ ብናልፍ ጠቁመው፤ ዘላቂ ሰላም እስኪመጣ ቀጣይነት ያለው ስራ ይሰራል ብለዋል።
ኢትዮጵያ አሁን ካለችበት ችግር ተላቃ በሀገሪቱ ዘላቂ ሰላምና ብሔራዊ መግባባት ይረጋገጥ ዘንድ የሰላም ሚንስቴር የ 10 ዓመት ፍኖተ ካርታ አዘጋጅቶ ለመተግበር ዝግጅት ላይ መሆኑንም ሚኒስትሩ ገልፀዋል::
ከዚህ በፊት የሰላም አምባሳደር የሆኑ ወጣቶችን አሰልጥኖ በየክልሉ የማሰማራቱ ስራም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
ምንጭ፡- የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ፌስቡክ ገፅ
Tartalom megjelenítő
የክቡር የሚኒስትሩ መልዕክት
አቶ መሐመድ እድሪስ መሐመድ የኢፊዲሪ የሰላም ሚኒስትር
የሰላም ሚኒስቴር በአዋጅ ከተሰጡት ዋና ዋና ተግባራት መካከል ሁለንተናዊ ዘላቂ ሰላም ማስፈን፣ ብሔራዊ መግባባትና አገራዊ አንድነትን ማጎልበት፣ የፌዴራል ሥርዓቱ የግንኙነት ማዕከል ሆኖ ማገልገል፣ ግጭቶችን አስቀድሞ መከላከልና ማስተዳደር ሲሆን እነዚህን ተግባርና ኃላፊነቶች በአግባቡ ለመወጣት የሚያስችሉ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን ያከናውናል።
ተጨማሪBeágyazott alkalmazások
Tartalom megjelenítő
ትንታኔ
አሰባሳቢ ትርክት ለብሔራዊ መግባባት
አፍራሽ ትርክቶች በግልም ሆነ በማኅበረሰብ ደረጃ ጎታች አስተሳሰቦችን ከማስረፅ በተጨማሪ ለምናስባቸው ግለሰባዊ፣ ማኅበረሰባዊና ሀገራዊ ግቦች ስኬትን ሳይሆን ውድቀትን ያመጣሉ።
ተጨማሪ ያንብቡየሰላም እሳቤ እና አስፈላጊነት
መዋቅራዊ የሰላም ግንባታ ጅምሮችን የሚያጎለብት፣ ማኅበረሰባዊ እሴቶችን ያማከለ፣ እና ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍሎች የሚያካትት ሰላምን ይበልጥ የሚያፀና ሥራ መሥራት ከሀገራችን ተሻግሮ ለቀጣናው ሁለንተናዊ ለውጦች ፋይዳው የላቀ ነው።
ተጨማሪ ያንብቡ